
Hosted by ዐቢይ ሀብታሙ · EN

''ያሉንን የተፈጥሮ ኃብቶች በአግባቡ እየተጠቀምን አይደለም። የግብርና መሠረተ ልማት ከፍተኛ ምርት ለማውጣት እንደ ጀርባ አጥንት የሚወሰድ ነው — መንግስታት ከፍተኛ ጥረት እያደረጉ መሆናቸው ቢታወቅም ከውጪ የሚሸመቱ ምግቦችን ለመቀነስ አሁንም ብዙ ነገሮች ይጠበቅባቸዋል '' ሲሉ በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ቴክኖሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ አዲሱ ፍቃዱ (ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ አብራርተዋል።ሁለት ጉዳዮች በሚቃኙበት የዛሬው ፕሮግራማችን በክፍል አንድ ከፍተኛ የተፈጥሮ ኃብት ያላት አፍሪካ ስለምን በከፍተኛ ሁኔታ ከውጪ ተሸምተው ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ ምግቦች ጥገኛ ሆነች ደግምስ ቀጣዩ ዘመናት ምን መምሰል አለባቸው ስንል በአርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የምግብ ቴክኖሎጂ ተባባሪ ፕሮፌሰሩ አዲሱ ፍቃዱ (ዶ/ር) ጋር ተወያይተናል። በክፍል ሁለት ደግሞ በአፍሪካ ቀዳሚ የኢንቨስትመንት መዳረሻ ናት። ከስኬቷ ጀርባ ያለውን ምስጢር እና ሌሎች ሀገራት ሊውስዱ የሚችሉ ተሞክሮዎችን ምሪሺየሳዊ የምህንድስና እና የከተማ ቄየሳ ባለሙያው ቪነሽ ቺንታራም አስረድተውናል። ሙሉ መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

''ዋሽንግተን መሪዎችን በመግደል እና ኃይሏን በመጠቀም ኢራንን በአጭር ግዜ ውስጥ አንበረክካለሁ ብላ አስባ ነበር። በተቃራኒው ኢራን ድብደባዎቹን ተቋቁማ፤ መከላከሏን ቀጠለች እንዲሁም የጦር ሜዳውን ወደ ባሕረ ሰላጤው፣ ወደ አረቦች እና ወደ ሌሎች የዓለም ክፍሎች አስፋፍታለች። በዚህም አሜሪካ የበላይነቷን አሳያለሁ ብላ ድክመቷን አጋልጣለች ”- የወራቤ ዩኒቨርስቲ መምህር መሃመድ አዎል ሀጎስ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል፡፡በዛሬው ሶቨርኒቲ ሶርስስ ፕሮግራም በክፍል አንድ የዓለም አሃዳዊ ዋልታ የኃይል ስርዓት እያከተመ ስለመሆኑ ከጂዮፖለቲካዊ አኳያ ከወራቤ ዩኒቨርስቲ መምህር መሃመድ አዎል ሀጎስ ጋር ተወያይተናል። በሁለተኛው ክፍል በአፍሪካ ያለውን የጸጥታ እና የውጭ ኃይሎች ጣልቃገብነት ጉዳይ ከሙከረም ሚፍታህ (ዶ/ር)፣ የኢትዮጵያ ሲቪል ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የፖሊሲ ጥናቶች ረዳት ፕሮፌሰር ጋር ቃኝተነዋል። በመጨረሻው ክፍል ከሚያዝያ 8-9 ፣ 2026 በአዲስ አበባ የተካሄደው የአደጋ ስጋት አስተዳደር አቅምን በተመለከተ ከቻርሎት ኖርማን፣ የጋና ብሔራዊ የአደጋ አስተዳደር ድርጅት የአየር ንብረት ለውጥ መላመድ እና የአደጋ ስጋት ቅነሳ ዳይሬክተር ጋር ዳሰነዋል።ሙሉውን መረጃ ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

ዓለም የባዮሎጂካል ብዝሃነት ዓለም አቀፍ ቀንን በፈረንጆቹ ግንቦት 22 ቀን ያከብራል።'' አፍሪካ ለአየር ንብረት ለውጥ የተጋለጠች አህጉር ነች፣ በእርግጥ አንድ ዓይንት ስነ ምህዳር አይደለም ያላት። ስለዚህ ይህ የሀገር በቀል እውቀት ለብዝሃ ህይወት ይጠቅማል። ብዝሃ ህይወት ስንል ብዙ ዝርያ ያላቸው እንስሳት፣ ዕፅዋትና ደቂቀ ነፍሳትን አንድ ላይ የያዘ ነው '' - ሲሉ የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ዋና ዳይሬክተሩ ሺቲ ጋተው(ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።በዛሬው ፕሮግራማችን በክፍል አንድ የአፍሪካን ስነ ኑረቶችና ብዝሃ ህይወትን ለመጠበቅ ሀገር በቀል እውቀቶች ያላቸውን ሚናዎች የአርባ ምንጭ ዩኒቨርሲቲ የአካባቢ ብዝሃ ህይወት ጥበቃ ዋና ዳይሬክተሩ ሺቲ ጋተው(ዶ/ር) ጋር ቆይታን አድርገናል። በክፍል ሁለት አፍሪካ በዓለም አቀፍ የሠው ሰራሽ አስተውህሎት ዕድገት ጉዞ ያላትን ቦታ ቴክኖሎጂ እንዲሁም የሰርቨር ቁጥጥርና አስተዳደር ባለሙያው ታደሰ ፀሃይነህ ጋር ቃኝተነዋል። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

''ራሺያኖች ሉዓላዊነታቸውን በመጠበቅ፣ ራሳቸውን በማስታጠቅ እና በአርበኝነት ረገድ በጣም ጥሩ ናቸው። ባህላቸውም በሚገባ የጎለበተ እና የተብላላ ነው። ስለዚህ አፍሪካዊያን ከእነርሱ ጋር ምንም ዓይነት የቅኝ ግዛት ግንኙነት ከሌላት ራሺያ ብዙ መማር ይችላሉ '' ሲሉ የእዮብዘር ዘውዴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህር ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ሁለት ጉዳዮችን በምንቃኝቀት ፕሮግራማችን በክፍል አንድ የራሺያ 81ኛው የድል ቀንን መሠረት በማድረግ ከፓን አፍሪካኒዝም አንድነት ጋር በማስተሳሰር የዮብዘር ዘውዴ በአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህር ጋር በስፋት እንወያያለን። በክፍል ሁለት ከፈረንጆቹ ግንቦት 7 - 8፣ 2026 በአዲስ አበባ ስለተከናወነው የአፍሪካ የማኅበራዊ ሚዲያ ተፅዕኖ ፈጣሪዎች ጉባዔን በተመለከተ እውቁ ጋናዊ ዩቱበር ዎዴ ማያ ሀሳቡን ያካፍለናል። ሙሉውን መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራም ያዳምጡ:

''አሁን ላይ ልጆች ላይ እየደረሰ ያለው ነገር አስፈሪ በሚባል ደረጃ እየሄደ ያለ ነው። የተለያዩ ጥቃቶች እየተፈፀሙ ነው። እነዚህ ልጆችም ለማይሆኑ ነገሮች እየተጋለጡ ይገኛሉ — የዲጂታሉ ዓለም ገደብ የለውም። ከስነልቦና፣ ከእውቀታቸውና ራሳቸውን መቆጣጠር ከሚችሉበት በላይ የሆኑ ነገሮችን እየተመለከቱ ለብዙ ነገሮች እየተጋለጡ ይገኛሉ። ጥፋቱ ከፍተኛ ነው ማለት እንችላለን - '' ሲል በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ምህንድስና መምህሩና የማኅበራዊ ሚዲያው ተጽዕኖ ፈጣሪና የመረጃ ሰጪ ይዘት ያላቸው ዜናዎችን በቲክቶክ የሚያጋራው ብሩክ ጫላ ለስፑትኒክ አፍሪካ አፍሪካ ተናግሯል ።ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው ዝግጅቱ በክፍል አንድ ታዳጊ አፍሪካውያን ህጻናትን ከሳይበር ጥቃት፣ ብዝበዛ እና ካልተፈለጉ ጫናዎች ስለመከላከል በአሶሳ ዩኒቨርሲቲ የሜካኒካል ምህንድስና መምህሩና የማኅበራዊ ሚዲያው ተጽዕኖ ፈጣሪና የመረጃ ሰጪ ይዘት ያላቸው ዜናዎችን በቲክቶክ የሚያጋረው ብሩክ ጫላ ዕይታውን ያጋራናል። ክፍል ሁለት እንደ ዓለም አቀፍ የገንዘብ ፈንድ እና የዓለም ባንክ ባሉ ተቋማት በደቡባዊ ዓለም ሀገራት ላይ የሚያሳድሩት ተጽዕኖን በደብረ ማርቆስ ዩኒቨርሲቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለም አቀፍ ግንኙነቶች መምህሩ ደረጄ መለስ ጋር እንወያያለን። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

''መሪዎችን መግደል፣ ዜጎችን መግደል፣ ሁሉም ነገር እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ግፍ ነው። እኛ የምንላችሁን ስሙ፣ እኛ ኃያላን ነን፣ ሁሉንም ነገር ማድረግ እንችላለን ነው የሚሉት። ኢራን በቀጥታ የተፈፀመባት ወረራ ነው -'' ሲሉ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በክፍል አንድ ሰሞነኛው የኢራን - አሜሪካ - እስራኤል ግጭትን መሠረት አድርገን በህገወጥ መንገድ በተለይም በውጭ ጣልቃ ገብነቶች ስለሚደረጉ የመንግስት ለውጥ ከሀገራት ሉዓላዊነት እና ህጋዊ አንድምታዎች አኳያ በራያ ዩኒቨርሲቲ የሰላም፣ ግጭትና ልማት መምህርና ተመራማሪው ዶ/ር አሌክሳንደር ኃይማኖት ጋር ተወያይተናል። በክፍል ሁለት ከሩሲያ - ኢትዮጵያ ንግድ ፎረም መነሻነት በሀገራቱ መካከል ያለ የሁለትዮሽ ንግድ ግንኙነትን ከዋሲሁን ፍቅሬ የኢትዮጵያ ንግድ እና ዘርፍ ማህበራት ምክር ቤት ፕሮዝዳነት ጽ/ቤት ኃላፊ ጋር ዳሰናል። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

'' የተባበሩት መንግስታት ድርጅት በተለይ ከጎርጎሮሲያኑ 2000 ወዲህ ከፍተኛ ችግሮች እየገጠሙት ይገኛል — የተቋቋመበትን የዓለም አቀፍ ሰላምና ድኅንነትን የማስፈን ተግባር በተቋቋመበት ዓለማ አስጠብቆ እየሄደ ነው ለማለት አዳጋች ነው። ስለዚህ ባለብዘ ወገን ስርዓት እየተፈጠረ ባለበት ዓለም ተገዳዳሪ አየሆኑ የመጡ ሀገራትን ያካተተ፣ ድምፃቸውንም የሚያስተጋባ መሆን አለበት'' - ሲሉ በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል መምህሩ ጃራ ሳሙኤል ከስፑትኒክ አፍሪካ ጋር ባደረጉት ቆይታ ተናግረዋል። ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው መርሃ ግብሩ በክፍል አንድ ዓለም ከነጠላ የፖለቲካ ስርዓትና አስተዳደር ወደ ባለብዙ ወገን ስርዓት እየተሸጋገረች ባለችበት በዚህ ወቅት የዓለም ሀገራትን በአንድ አቅፎ የያዘው የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ቀጣይ እጣፈንታ ምን ሊመስል ይችላል የሚለውን ጉዳይ በአርሲ ዩኒቨርሲቲ የህግ ትምህርት ክፍል መምህሩ ጃራ ሳሙኤል ጋር ዳሰነዋል።በክፍል ሁለት በቅርብ ወደ ትግበራ የገባው የሰው አልባ ፖሊስ ጣቢያ ወይም ‘ስማርት ፖሊስ ስቴሽን ጉዳይ ኢንስፔክተር አንድነት ሲሳይ፤ በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የቴክኖሎጂ ኦፕሬሽን ዋና ክፍል ኃላፊ አጠቃላይ ቅኝት ያደርጉልናል፡፡ ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

''ስፔስ ሳይንስን ልዩ የሚያደርገው የማናውቀውን ነገር ለማወቅ ጥረት የምናደርግበት ነው። በዚህ ረገድ የስፔስ ሳይንስ ምርምር መስመር እንዲይዝ ዩሪ ጋጋሪን መሰረት የጣለ ታላቅ ሰው ነው - ሲሉ የዘርፉ ተመራማሪው አለምዬ ማሞ(ዶ/ር) ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል።" በዛሬው ፕሮግራም በክፍል አንድ በየዓመቱ በጎርጎሮሲያኑ መጋቢት 12 የሚከበረውን የሰው ልጅ ለመጀመሪያ ጊዜ ወደ ህዋ የተጓዘበትን ቀንና የህዋ ሳይንስ ጉዳይ ከኢትዮጵያ ኑውክላር አነርጂ ኮሚሽን ምክትል ኮሚሽነሩ አብድረዛቅ ኡመር እና የስነ ህዋ ተመራማሪው ዶ/ር አለምዬ ማሞ ጋር ጥልቅ ምልከታ ተከናውኗል። በመካከለኛው ግጭት ሳቢያ በንግድና ፋይናንስ ላይ ተፅዕኖ ቢፈጥሩም የኢትዮጵያ ብሔራዊ ባንክ ጫናውን ለመቋቋም የገንዘብ ፖሊሲውን እንደሚያስቀጥል ስለመግለፁ ከባንክ፣ ኢንሹራንስ እና የማርኬቲንግ ባለሙያው አስቻለሁ ታምሩ ጋር የምናደርገው አጭር ቆይታም የፕሮግራማችን ሌላኛው አካል ነው። ሙሉውን መረጃ ለማግኘት ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

''እኛ ፋሲካ የምንለው የክርስቶስ ትንሣኤ በዓል፣ በአጠቃላይ በክርስትና ትውፊት ውስጥ በተለይ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ከዋና ዋናዎቹ እና እጅግ በጣም አስፈላጊ ከሆኑት በዓላት አንዱ ነው — የመጽሐፈ ሄኖክ እና ኩፋሌ፣ በተለይም ደግሞ የሄኖክ መጽሐፍ፣ ሙሉ ይዘቱ በግዕዝ ቋንቋ፣ በኢትዮጵያ ብቻ ይገኛል። ከጥቂት መቶ ዓመታት በፊት ጄምስ ብሩስ የተባለ አንድ እንግሊዛዊ ተጓዥ የሄኖክን መጽሐፍ ከጣና ሐይቅ አካባቢ በስጦታነት ተቀብሎ ወደ አገሩ ወስዶታል። ለጉብኝቱ እና ለኢትዮጵያ ቆይታው እንደ ስጦታ በወቅቱ ከነበሩት የኢትዮጵያ ንግሥቶች በአንዷ፣ በንግሥት ምንትዋብ ተሰጥቶታል።'' - ሲሉ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያንየነገረ መለኮት ምሁር መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ፈለቀ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። በዛሬው ልዩ የሶቨርኒቲ ሶርስስ ዝግጅታችን፣ የትንሳኤ በዓልን መሠረት በማድረግ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን መጽሐፍ ቅዱሳዊ መሠረቶችን እንዲሁም ከምዕራባዊያን የበዓል አከባበር ጋር ያለውን ልዩነት እንግዳችን መምህር ዳንኤል ሰይፈሚካኤል ፈለቀ ያስረዱናል። ሙሉውን መረጃውን ለማግኘት በእንግሊዘኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ:

''የመካከለኛው ምሥራቅ በተለይም የአረብ ሀገራት የውጭ ግንኙነታቸው፣ ከፀጥታ ጋር የተገናኘው በአሜሪካ ላይ ጥገኛ እንደሆነ እናውቃለን — የአረብ ሀገራት በአንድም በሌላ መንገድ የሚኖራቸው የመልስ ምት ወሳኝ ነገር ነው'' - በወልዲያ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለምአቀፍ ግንኙነት መምህሩ መሃመድ ሰዒድ ለስፑትኒክ አፍሪካ ተናግረዋል። ሶቨርኒቲ ሶርስስ በዛሬው መርሃ ግብሩ በክፍል አንድ በግጭት ወጥመድ ውስጥ የሚገኙት የአረብ ሀገራትን መነሻ በማድረግ የምዕራባዊያን ተፅዕኖዎችና የድሮን ጦርነቶችን በወልዲያ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስና ዓለምአቀፍ ግንኙነት መምህሩ መሃመድ ሰዒድ ጋር እንዳስሳለን። በከፍል ሁለት ስለኢነርጂ እና ኢንዱስትሪያልዜሽን መጎልበት በተለይም በአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠናን በሚመለከት በዘርፉ ኤክስፐርት ከሆኑት አበጀ መንገሻ ጋር እንወያያለን። ሙሉውን መረጃው ለማግኘት በእንግሊዝኛ ቋንቋ የቀረበውን ፕሮግራሙን ያዳምጡ: